በሀገረ ቤልጅየምና በዙሪያዋ ለምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን በሙሉ፤
በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእናታችን በወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም ስም መንፈሳዊ ሰላምታችንን እያስቀደምን: እንኳን ለእናታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ። የየካቲት ኪዳነ ምህረትን በዓል በዕለቱ የካቲት 16፣ 2005ዓ.ም (Feb 23, 2013) ከዋዜማው (የካቲት15, Feb.23) ጀምሮ; ከየአጥቢያ ቤተክርስቲያን በሚመጡ አባቶች እና ምእመናን በሚገኙበት ሌሊት በማኅሌት እና ጠዋት በቅዳሴ በደመቀ ሁኔታ ይከበራል። ቤተክርስትያኗ ከዋዜማው ምሽት 22፡00 ሰዓት ጀምሮ ክፍት ስለምትሆን በሰዓቱ ተገኝተው ከልዩ ልዩ የአዳር መርሐ ግብሮች ተካፋይ እንዲሆኑና ሌሎችንም እንዲጋብዙ ቅድስትቤተ-ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች። ሕንፃ ቤተ-ክርስትያኑ ከእኩለ ቀን (11፡30) በሗላ ለሌላ አገልግሎት ስለሚፈለግ በሰዓቱ ቀደም ብለው በመገኘት የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ በትህትና እንጋብዛለን። ይህ መልዕክት የማይደርሳቸውን ምዕመናንንም በመቀስቀስ የበረከቱ ተሳታፊ እናድርጋቸው።የአምላካችን ረድኤት የቅድስት ኪዳነ ምሕረት አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁን።
No comments:
Post a Comment