Pages

ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን


ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን መግቢያ
በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ
እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሁሉ በሀብት ስቦ በረድኤት አቅርቦ ወደ ራሱ ይጠራቸዋል ፤ ያቀርባቸዋል፡፡ የተጠሩት ደግሞ በንዑሰ ክርስቲያንነት ደረጃ ቃለ እግዚአብሔርን እየሰሙ ከቆዩ በኋላ አዲስ ሕይወትን እንዲቀዳጁና ጸጋ መንፈስ ቅዱስን እንዲያገኙ የሚያበቃቸው ሌላ መንገድና ሥርዓት አስፈላጊ ስለሆነ ጌታ ራሱ አዘጋጅቶላቸዋል ፤ ሁላችንንም በዚህ መንገድ እንድንሄድ አዞናል፡፡ መንገድ የተባለውም ቃሉን ሰምቶ መፈጸምና ያዘዘንን የቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት ሁሉ መፈጸም ነው፡፡

ሰባቱ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን
                                                                                                                            በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዓይ

ቤተ ክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ የጸጋው ግምጃ ቤት ስለሆነች መስቀል ላይ የተሰጠውን አምላካዊ ጸጋ በእምነት ለሚቀርቧት ሁሉ ታድላለች ፣ ትምህርቷን አምነው የተቀበሉ ሁሉ የዚህ ጸጋ ተካፋዮች ናቸው፡፡ ይህን ጸጋ ለምዕመናን የምታድልባቸውን መሳሪያዎች ምሥጢራት ትላቸዋለች፡፡
ሙሉውን እዚህ በመጫን ያንብቡ

ሰባቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን


በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ
ለሥጋ ሕይወታችን ልደት ፣ እድገትና ሌሎችም ነገሮች እንዳሉት መንፈሳዊ ሕይወታችንም እንደዚሁ ይኸንኑ የሚመስሉ ሁኔታዎች አሉት፡፡ በዚህ መሠረት አንድ ሰው መንፈሳዊ ልደትን የሚያገኘው በእምነትና በምሥጢረ ጥምቀት እንደሆነ እንረዳለን፡፡ ከዚህም ቀጥሎ ምሥጢረ ሜሮንና ምሥጢረ ቁርባን በተከታታይ ይፈጸማሉ፡፡ እነርሱም መንፈሳዊ ልደታችንንና እድገታችንን ከፍጹምና ያደርሱታል፡፡የአገልግሎትና የአንድነት ጸጋ የምናገኝባቸው ደግሞ ምሥጢረ ክህነትና ምሥጢረ ተክሊል ናቸው፡፡







No comments:

Post a Comment